የድረ ገፅ ደንብ ! ! !

                  

የድረ ገፅ ስያሜ:-    

  1. ዓላማ

  2. ተግባር

  3. መረሐ ግብር

  4. መምሪያዎች

  5. ስያሜ

  6. ዓርማ

 

  1. ዓላማ፣

 

በጠቅላይ ሚኒስትር ሄሮድስ መለስ ዜናዊ የሚመራው ጎሳዊና ፋሽስታዊ አገዛዝን ግባተ መሬት

ለማፋጠን በሚካሄደው ዲሞክራሲያዊ ትግል፣

 - የግንዛቤን አድማስ በማስፋፋት የህሊናን መሰናዶ ለማሟላት፣

 - የሕዝቡን ዲሞክራሲያዊ ትግል በሀሳብ ለማገዝ፣

 - እንዲሁም ሁለገብ የሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮችን በብዕር ለዛ ለመቃኘት ይሆናል።

በተጨማሪም የ 21ኛውን ምዕተ ዓመት ተረካቢ የሆኑ ልጆችን በሚመለከት በጣም በጥቂቱ የመክፈቻ መሠረት ለመጣል ( የቻለ አስፍቶ ሊቀጥል ይችላል፣ ማሳው ድንግል ነውና )፣

 

  2. ተግባር፣

 

 2.1 የድርሻችንን ለመወጣት ድልድይ መዘርጋት / መንገድ ለመክፈት /

2.2 የልምድ፣ የዕውቀት እና የተመክሮ ምክለት ለመፍጠር፣

2.3 የስደትን ሕይወት ለማናገር፣

2.4 የሰው ልጅ የነቃው የህሊና ክፍል በእህልና በመጠጥ ብቻ አይኖርም:: የሰው  ልጅ የነቃው የህሊና  

    ክፍል ትልቅ ውስብስብ ረቂቅ ምጥቅ ልዩ ማሳ ነው:: ማሳው  ደግሞ በመስኖ መልማት አለበት::  

    መስኖው ደግሞ ጥበብ ነው:: ጥበብ ደግሞ ረቂቅ የሆነ ቅዱስ ፀጋዊ መንፈስ ነው:: ስለዚህ  እኛ እና  

    የጥበብ መንፈስን ጥበብን ወይንም ጥበብና እኛን በሰማንያ እንደአቅማችን ለማጋባት ነው::

 

3. መረሐ ግብር፣

 

እንደሚታወቀው መርሀ ግብር መሪ የተግባር ትልም ማለት ነው::

ለአንድ ድርጅት ወይንም ለግል ሕይወትም መርሀ ግብር ያስፈልገዋል:: መርሀ ግብር የሌለው አካል ዓይን የለውም:: ዓይን ካልኖረምደግሞ የፈለገ ዓይነት ብቃት ቢኖረው አይደለም ሌላውን እራሱን እንኳን መምራት አይችልም::

መርሀ ግብር የተግባር ትልም፣ መሪ፣አቅጣጫ አመልካች መንገድቀያሽ መሀንዲስ ነው:: ስለሆነም ድህረ ገጻችን ሦስት ደረጃ ( ምዕራፍ)ያላቸው ትልሞች አሉት።

 

3.1 የአጭር ጊዜ _ ከአንድ ሳምንት እስከ አንድ ወር፣

3.2 የመካከለኛ ጊዜ _ ከአንድ ወር አስከ አንድ ዓመት፣

3.3 የረዥም ጊዜ _ ከአንድ ዓመት እስከ አምስት ዓመት፣

 

አሁን በአለን አቅምና ሁኔታ በአጭር ጊዜ መርሀ ግብራችን መንቀሳቀስ አንጀምራለን:: ማለትም በእጃችን ባሉ ነገሮች ዙሪያ መርሐ ግብራችን አኃዱ ይላል:: ቢያንስ ለእያንዳንዱ መምሪያ በወር አንድ ጽሑፍ ማውጣት የሚያስችል ሙሉ መሰናዶው ተጠናቋል::

 

4. መምሪያዎች

ቃና

ማዕዶት

አብረታት

የሎሬት ተስፋ

ዕድምታ  

5. ስያሜ፣- 

  

   ፀጋዬ ድህረ ገፅ፣

6. ዓርማ፣- 

   

   በአለም ካርታ ውስጥ የአፍሪካ ካርታ፣ በአፍሪካ ካርታ ውስጥ የኢትዮጵያ 

    ካርታ፣-  በኢትዮጵያ ካርታ ውስጥ የብላቴን ጌታ ሎሬት ፀጋ ገ/መድኅን ፎቶ፣

6.1 የዓርማ ትርጉም

   

   . የዓለም ካርታ መዐቀፉ የሆነበት ምክንያት ጥበብ ድንበር፣ ወሰን የማይገድበው በመሆኑ፣

   . ድህረ ገፃችን ዓለም አቀፋዊ ስለሆነ፣

   . የሌሎች ሀገር ፅሑፎች፣ ግጥሞች ልናስተናግድ ሀሳቡ ስላለን ነው::

  >> Page two >> Page 3 >> Page 4

 

 

<< Back to Tesfa << Back to Menu        write your Comments